ኦዲዮ መጽሐፍ ቅዱስ አማርኛ ውስጥ APK
[ Red Appz ] [Trusted App ]
ኦዲዮ መጽሐፍ ቅዱስ አማርኛ ውስጥ | ብሉይ ኪዳን ና አዲስ ኪዳን. یہ ایپ 7 مارچ 2017 کو جاری کی گئی تھی، تازہ ترین ورژن 4.0.0 ہے، 3 اگست 2023 کو اپ ڈیٹ کی گئی۔ اس ایپ کو +10 ہزار سے زیادہ بار ڈاؤن لوڈ کیا گیا ہے، جس کی اوسط درجہ بندی 4.6⭐ ہے۔
ایپ ڈاؤن لوڈ کریں: ኦዲዮ መጽሐፍ ቅዱስ አማርኛ ውስጥ
✅ بہترین سیکیورٹی اور مسلسل اپ ڈیٹس کے لیے ہم سختی سے تجویز کرتے ہیں کہ یہ ایپ براہ راست Google Play سے انسٹال کریں۔
تاہم، اگر آپ APK فائل کو براہ راست انسٹال کرنا پسند کرتے ہیں تو آپ اسے یہاں سے ڈاؤن لوڈ کر سکتے ہیں۔ فراہم کردہ فائل 100٪ اصل اور غیر ترمیم شدہ ہے، جو Google Play ورژن کی طرح ہی سیکیورٹی فراہم کرتی ہے۔
APK فائل، تازہ ترین یا پرانا ورژن ڈاؤن لوڈ کرنے کا انتخاب کریں
[ تمام ورژنز ]
اس ایپ ኦዲዮ መጽሐፍ ቅዱስ አማርኛ ውስጥ میں کیا خاص ہے؟
سرکاری تفصیل
መጽሐፍ ቅዱስመጽሐፍ ቅዱስ ነብያትና ሓዋሪያት በመንፈስ ተመርተው የጻፉት የክርስቲያኖች እምነት መጽሓፍ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በብሉይ ኪዳንና በአዲስ ኪዳን ተከፍሎ 66 መጻሕፍት አሉት። ከነዲዩትሮካኖኒካል መጻሕፍትም ጋራ የመጻሕፍት ቁጥር 81 ነው።
የመጽሐፍ ቅዱስ ምንነት
በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተለመደው «ባይብል» የሚለው ቃል ከጥንቱ የኮይነ ግሪክኛ ቋንቋ የተወሰደ ሲሆን ቃሉ የተገኘበት τὰ βιβλία /ታ ቢብሊያ/ የሚለው ሀረግ «መጽሐፍቱ» ወይም «ትንንሽ መጽሐፍት» ተብሎ ሊተረጎም ይችላል። የዚሁም ቃል መነሻ ከግሪኩ ስም Βύβλος /ቢውብሎስ/ (ፓፒሩስ ወይም የወረቀት ተክል) ሲሆን ይሄ ቃል ፓፒሩስ ከተነገደበት ከተማ ጌባል ስም መጣ።
መጽሐፍ ቅዱስ ለአይሁድና ክርስትና እምነት የእምነት መሰረት የሆኑ ትናንሽ መጽሐፍትን የያዘ አንድ ጥራዝ ነው። በተለምዶ «ብሉይ ኪዳን» በመባል የሚጠራውና በአይሁዳውያን በ24 እና በክርስቲያኖች በ39 መጽሐፍት የሚከፈለው የመጽሐፍ ቅዱስ የመጀመሪያ ክፍል በመጀመሪያ በአብዛኛው የተጻፈው በጥንታዊው የዕብራይስጥ ቋንቋ ሲሆን የተጻፉበት ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት የተወሰኑ መቶ አመታት ቀደም ብሎ እንደሆነ ይነገራል። እነዚህን መጽሐፍት የጻፉት በወቅቱ የነበሩ የታመኑ አይሁዳውያን ወይም እስራኤላውያን ናቸው። የመጨረሻዎቹን 27 መጻሕፍት በግሪክኛ የጻፏቸው ክርስቲያኖች ሲሆኑ «አዲስ ኪዳን» በመባል በሰፊው ይታወቃሉ። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኘው ማስረጃም ሆነ በጣም ጥንታዊ የሆኑት ወጎች እንደሚጠቁሙት እነዚህ 66 መጻህፍት የተጻፉት ግብጽ ኃያል ከነበረችበት ጊዜ አንስቶ ሮም የዓለም ኃያል መንግስት እስከ ነበረችበት ዘመን ባሉት 1600 ዓመታት ውስጥ ነው።
በካቶሊክ ቤተክርስቲያን እምነት መሰረት ከ66ቱ መጽሐፍት በተጨማሪ የተካተቱ የተወሰኑ መጽሐፍት ሲኖሩ፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እነዚህ ተጨማሪ መጻሕፍት (ዲዩቴሮካኖኒካል በመባልም ይታወቃሉ) በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተካተቱትን መጻሕፍት ቁጥር ወደ 81 ያደርሱታል።
ከክርስቶስ ስብከት ቀጥሎ ምዕመናን የሆኑት ለረጅም ዘመን ተጨማሪ መጻሕፍቱን ከነመጽሐፈ ሄኖክና ኩፋሌ ያንብቡ ነበር። የአይሁድ ሰንሄድሪን ረቢዎች በ100 ዓ.ም. አካባቢ በተለይም ረቢ አኪቫ በን ዮሴፍ እነዚህን ተጨማሪ መጻሕፍት ከዕብራይስጥ ቅጂ አጠፉ። እስካሁንም ድረስ በዕብራይስጥ ትርጉም አይታወቁም። አዲስ ኪዳን ከተጻፈ በኋላ፣ ብዙ አጠያያቂ ወንጌሎችና የሌሎች እምነቶች ጽሑፎች ደግሞ ሊሠራጩ ጀመር። ግኖስቲክ የተባለው እምነት ተከታዮች በተለይ ብዙ ሥነ ጽሑፍ ፈጠሩ፣ ይህ ግን ከኦርቶዶክስ ወንጌል የተዛቡ ትምህርቶች ነበር። በ170 ዓ.ም. በክርስትያኖች ዘንድ የቱ መጻሕፍት ትክክለኛ ቅዱሳን መጻሕፍት ናቸው? የሚል ጥያቄ ይነሣ ጀመር። መሊቶ ዘሳርዲስ የተባለ ጳጳስ በዚያን ጊዜ ወደ ኢየሩሳሌም መጻሕፍት ቤት ጉዞ አድርጎ የ ዕብራውያን መጻሕፍት ምን ምን እንደ ነበሩ ዘገበ። ተጨማሪ መጻሕፍቱ ከዚያ በፊት ስለ ጠፉ አልተዘገቡም። ስለዚህ ከዚህ በቀር ምንም ያልተዘረዘሩት ብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ትክክለኛ አይሆኑም የሚል ሀሣብ በሮሜ መንግሥት ክርስቲያኖች ተነሣ። ይህም የአይሁዶች ቀኖና በንቅያ ጉባኤ (317 ዓ.ም.) በሮሜ መንግሥት ለክርስቲያኖች ጸና።
-----------------------------
ብሉይ ኪዳን
ኦሪት ዘፍጥረት
ኦሪት ዘጸአት
ኦሪት ዘሌዋውያን
ኦሪት ዘኍልቍ
ኦሪት ዘዳግም
መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ
መጽሐፈ መሣፍንት
መጽሐፈ ሩት
መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ
መጽሐፈ ሳሙኤል ካል
መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ።
መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ።
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ።
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ።
መጽሐፈ ዕዝራ።
መጽሐፈ ነህምያ።
መጽሐፈ አስቴር።
መጽሐፈ ኢዮብ።
መዝሙረ ዳዊት
መጽሐፈ ምሳሌ
መጽሐፈ መክብብ
መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን
ትንቢተ ኢሳይያስ
ትንቢተ ኤርምያስ
ሰቆቃው ኤርምያስ
ትንቢተ ሕዝቅኤል
ትንቢተ ዳንኤል
ትንቢተ ሆሴዕ
ትንቢተ ኢዮኤል
ትንቢተ አሞጽ
ትንቢተ አብድዩ
ትንቢተ ዮናስ
ትንቢተ ሚክያስ
ትንቢተ ናሆም
ትንቢተ ዕንባቆም
ትንቢተ ሶፎንያስ
ትንቢተ ሐጌ
ትንቢተ ዘካርያስ
ትንቢተ ሚልክያ
አዲስ ኪዳን
የማቴዎስ ወንጌል
የማርቆስ ወንጌል
የሉቃስ ወንጌል
የዮሐንስ ወንጌል
የሐዋርያት ሥራ
ወደ ሮሜ ሰዎች
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች
2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች
ወደ ገላትያ ሰዎች
ወደ ኤፌሶን ሰዎች
ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች
ወደ ቆላስይስ ሰዎች
1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች
2ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች
1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ
2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ
ወደ ቲቶ
ወደ ፊልሞና
ወደ ዕብራውያን
የያዕቆብ መልእክት
1ኛ የጴጥሮስ መልእክት
2ኛ የጴጥሮስ መልእክት
1ኛ የዮሐንስ መልእክት
2ኛ የዮሐንስ መልእክት
3ኛ የዮሐንስ መልእክት
የይሁዳ መልእክት
የዮሐንስ ራእይ
ماخذ: سرکاری ایپ کی تفصیل Google Play سے حاصل کی گئی۔ صرف حوالہ کے لیے۔
دیگر کتابیں اور حوالہ ایپس
کچھ دیگر کتابیں اور حوالہ ایپس جن کی آپ کو ضرورت ہو سکتی ہے